Sunday, September 15, 2013

መስከረም 5



በዚህች ቀን የከበረች ቅድስት ሶፍያ በከሃዲው ንጉስ በከላድያኖስ ዘመን ከሁለት ሴት ልጆቿ ጋር በሰማዕትነት አረፈች።ይህች ቅድስት መጀመሪያ ጣኦት አምላኪ ነበረች በኃላም ክርስቶስን ወደ ማምለክ ተመለሰች በዚህም ንጉሱ ተቆጣ ብዙ ጸዋትኦ መከራ አደረሰባት በመጨረሻም አንገቷን ቆረጣት አስከትሎም ልጀቿ በርናባንና አክሳስናን ገደለ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ። ይህ ከሀዲ ንጉስ ሞቶ ደገኛው ንጉስ ቆስጠንጢኖስ በነገሰ ጊዜ ሰጋቸውን አፍልሶ ትልቅ ቤተክርስቲያን ሰርቶላቸዋል።በረከታቸው ይደርብን፡

No comments:

Post a Comment