Thursday, October 31, 2013

ጥቅምት 17


ጥቅምት 17
የቀዳሚ ሰማዕት የሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ የተሾመበትን ቀን ቤተክርስቲያን ታከብራለች፤መስከረም 15 ፍልሰተ አጽሙ ነው ጥር 1 እረፍቱ ነው፤ እነዚህ 3 ቀናት ሰማዕቱ በሰፊው ይዘከርባቸዋል። ቅዱስ እስጢፋኖስ አባቱ ስምኦን እናቱ ማርያም ስና ይባላሉ፤የአብርሃም ዘር አይሁዳዊ ናቸው ልጃቸውን በጥበብ አሳደጉት፤ እስጢፋኖስ ማለት ወደብ ጸጥታ ማለት ነው። ምነዋ ቀዳሚ ሰማዕት ተባለ ቀደምት ነብያት በመጋዝ ተሰንጥቀው እንደ ሽንኩርትም ተቀርድደው የለም ወይ ቢሉ ከጌታችን እርገት በኃላ የመጀመሪያው ሰማዕት እርሱ ስለሆነ ነው፤ ሊቀ ዲያቆናት ያሰኘው ቅሉ በሐዋርያት ስራ 6፤5 ከተመረጡት 7 ዲያቆናት አለቃቸው ስለሆነ ነው። አይሁድ አማጽያን ሊሞግቱት በሸንጎ ተሰበሰቡ መጽሐፍ እንደመሰከረው እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም ይላል፤ “አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ” ብሎ በግልጽ ዘለፋቸው ስለ ጌታችን መሰከረ በዚህም ተቆጡ ድንጋይ ጨበጡ በግፍ ገደሉት ይቅር በላቸው እያለ ነፍሱን ሰጠ፤ ጥቅምት 17 ይህን ቀን የሰማዕቱ ታቦት በሚገኝበት ሁሉ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።

LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment