Thursday, October 31, 2013

ጥቅምት 19

ጥቅምት 19
በዚህች ቀን ጻድቁ ንጉስ ይምርሃነ ክርስቶስ አረፈ፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው በላስታ ነግሶ የነበረው ንጉስ ጠቢባንን ይሰበስብና ከኔ በኃላ የሚነግሰው ማን ነው ? ብሎ ይጠየቃቸዋል እነርሱም የወንድምህ ልጀ ይምርሃነ ክርስቶስ ነው ይሉታል፤ልጂቼ እያሉ እንዴት እርሱ ይነግሳል ብሎ ይናደዳል፤ ሊገድለውም ይፈልገዋል፤ ይምርሃነ ክርስቶስም ፈርቶ ወደ እየሩሳሌም ይሰደዳል፤ በዚያም የሌዊ ነገድ የሆነችውን ቅድስት ህዝባ የምትባል ሴት ያገባል ቅስናም ተቀብሎ ማገልገል ይጀምራል፤ከረጀም ጊዜ በኃላ የሚያሳድደው ንጕሰ ሲሞት ወደ አገሩ ኢትዮጵያ ይመለሳል፤ ህዝቡንም ወንጌል ሲያስተምር ድውያንን ሲፈውስ አይተው የአገር ሸማግሌዎች ተሰብስበው ስምህ ማን ነው ይሉታል ይምርሃነ ክርስቶስ እባላላሁ ከነገስታቱ ወገን ነኝ ይላቸዋል፤ እነርሱም በጣም ተገረሙ፤ ምን አስገረማቸው ቢሉ ይምርሃነ ክርስቶስ የሚባል ደገኛ ንጉስ ሲነግስ ሃይማኖት ይቀናል ፍርድ ይስተካከላ፤በዘመኑ ብዙ የውጭ አገር ህዝቦች ወደ ኢትዮጰያ ይጎርፋሉ የሚል ትንቢት ነበርና፤ በእግዚያብሔር ፈቃድ ቀብተው አነገሱት፤እርሱም ንግስናን ከክህነት ጋር አጣምሮ ህዝቡን በፍቅር አያገለገለ ኖረ። የሚገርመው ቤተመቅደስ ገብቶ ሲቀድስ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ሰማያዊ ህብስትን ሰማያዊ ጽዋን ይዞለት ይመጣል ያንን የቅዳሴ ጸሎት አድርሶበት ለህዝቡ ያቆርብ ነበር፤ መልአኩ ለ 22 ዓመት ሳቋርጥ አምጥቶለታል፤ ይህ ቅድስናው በዓለም ተሰማ ከሮም ከግብጽ ከግሪክ 5470 ክርስቲያኖች ወደርሱ መጥተው በእጁ ይህንን ሰማያዊ ህብስት ተቀብለዋል፤ እንዴት መጣችሁ ብሎ ይጠይቃቸዋል፤ መልከጼዴቅ የሚባል በበርሃ የሚኖር አንድ ባህታዊ የእግዚያብሔር መልአክ ሰማያዊ ህብስት ይዞ ሲወርደ ያያል ለየትኛው መነኩሴ ልትሰጥ ነው ብሎ ይጠይቀዋል እርሱም ለመነኩሴ አይደለም ለንጉስ ነው ይለዋል፤ ምን አይነት ቅዱስ ንጉስ ቢሆን ነው ሰማያዊ ህብስት የሚወርድለት ይህን ንጉስ ማየት እፈልጋለሁ ይለዋል መልአኩም አንተ የእረፍትህ ቀን ደርሷል አታየውም ብሎት ይሄዳል፤ እርሱም እኛን ጠርቶ ይህንን ነገረን ወደ አንተም መጣን ብለው የአመጣጣቸውን ነገር ነግረውታል፤እነዚህ ክርስቲያኖች ይህን ያየ አይናችን ሌላ አያይም ብለው ወደ አገራቸው ሳይመለሱ እዚያው ላስታ ቡግና ኑረው እዚያው አርፈዋል አጽማቸው ዛሬም ድረስ ሳይፈርስ ሳይበሰብስ ይምርሃነ ክርስቶስ ባነጸው ቤተክርስቲያን በስተምዕራብ አቅጣጫ ይገኛል፤ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ለ 41 ዓመት በቅድስና በተጋድሎ ህዝቡን ሲመራ ኖሮ በ 97 ዓመት ከ 5 ወሩ በዛሬዋ ቀን አረፈ፤ ይህ ቅዱስ አባት በባህር ላይ ያነጸው ቤተክርስቲያ እጅግ የሚያስገርም ነው የላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በ 80 ዓመት ይቀድማል፤ ይህን የመሰለ ህንጻ በዚያን ዘመን አይደለም ለመስራት ለማሰብም ይከብዳል፤ ይህ ህንጻ ከከበሩ ድንጋዮች ነው የተሰራው በሩ አርዘ ሊባኖስ ከሚባል እጽ የተሰራ ሲሀን የግብጽ ንጉስ ነው የላከለት ግድግዳው በእንቁ የተንቆጠቆጠ ነው፤ በውስጡ የእመቤታችን፤ የቅዱስ ቂርቆስ፤ የጊዮርጊስ፤ የሩፋኤልና የራሱ የይምርሃነ ክርስቶስ ታቦታት አሉ፤ እናቶቻችን ወደዚህ ቦታ ሲሄዱ “”እላዩ አረንÙዴ ውስጡ ባህር ይምርሃነ ክርስቶስ የዋሻው ደብር’’ እያሉ የሚዘምሩት ለዚህም አይደል፡፡ ይህን ቦታ ለማየት ያብቃን ከበዓሉም በረከት ያሳትፈን፡፡
LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment