Thursday, October 31, 2013

ጥቅምት 2

በዚህች ቀን ደገኛው አባት አባ ህርያቆስ አረፈ። ይህ አባት ትውልዱ ብህንሳ ነው፤አልተማረም ግን በትሩፋት የጸና ደገኛ አባት ነው፤ የገዳሙ አበ ምኔትም ነበር፤ ልክ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም የእመቤቴ ምስጋናዋ እንደ ባህር አሸዋ እንደ ሰማይ ኮከብ በዝቶልኝ እንደ ምግብ ተመግቤው እንደ መጠጥ ጠጥቼው እንደ ልብስ ለብሼው በኖርኩኝ እያለ ይመኝ ነበር። በብህንሳ ያሉ አብዛኞቹ መኖኮሳት ይጠሉት ይንቁት ነበር ምነዋ ቢሉ ስርዓት ያጸናባቸው ነበር፤ከዕለታት በአንዱ ቀን በምን እንሻረው ብለው አሰቡ አስበውም አልቀሩም ቀድሰህ አቁርበን አሉት፤እመቤታችንን አደራ እንዳታሳፍሪኝ ብሎ ሊቀድስ ገባ፤ የለመኗትን የማትነሰ እመቤታችን አዲስ እንግዳ ድርሰት ገለጸችለት ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ ልቦናዬ በጎ ነገርን አወጣ ብሎ ወይእዜኒ ንሰብሖ እስከሚለው ድረሰ ሰተት አድርጎ ተናገረ፤ በዙሪያው ያሉት የሚወዱት መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እንዲህ ያለ ሚስጢር ከሩቅ ብእሲ አይገኝም አሉ፤ ገሚሶቹ የሚጠሉት ደግሞ አናናቁበት በዚህም ተከራከሩ ጽፈው ደጉሰው ከህሙም ላይ ጣሉት ድውይ ፈወሰ ይልቁንም ሙት አስነስቷል። 14ኛ ቅዳሴ አድርገው ይዘውታል። አባ ህርያቆስ ከአቡነ አረጋዊ ጋር ሆነው በርካታ መጽሐፍትን ይዘው ወደ ኢትዮጰያ እንደመጡ ህዝቡንም እንዳስተማሩ የጥር ድርሳነ ኡራኤል ላይ ተጽፎ ይገኛል፤ በድጋሚ ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እመቤታች አዛቸው አክሱም መጥተው ከቅዱስ ያሬድ ጋር ተገናኝተዋል አንተ ቅዳሴየን አንተ ደግሞ ውዳሴየን ነግራቹት በዜማ ያድርስ ብላቸው እነሱም ነግረውት አድርሶታል፤ አባ ህርያቆስ በንጽህና በቅድስና ኖሮ ጥቅምት በባተ በሁለተኛው ቀን በክብር አረፈ፤ የዚህ ደገኛ አባት በረከት ይደርብን።
LIKE >>> https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment