Thursday, October 31, 2013

ጥቅምት 6



ወበዛቲ ዕለት ... ጥቅምት 6

በዚህች ቀን ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት አቡነ ጰንጠሌዎን አረፉ፤ እኚህ ጻድቅ ልክ እንደነ አቡነ አረጋዊ ከሮም ከነገስታት ወገን ናቸው መንግስታቸውን ክብራቸውን ትተው ወደ ኢትዮጰያ መጡ ለጥቂት ጊዜ ዘጠኙም አብረው ኖሩ ከዚያ በኋላ ለየብቻ መኖር ይሻለናል ብለው ሁሉም ተበታተኑ አቡነ አረጋዊ ወደ ደብረ ዳሞ አቡነ ገሪማ ወደ መደራ ሌሎችም በየአቅጣጫው ሄዱ እኚህ አቡነ ጰንጠሌዎን ደግሞ አክሱም አቅራቢያ ተራራ ላይ ወጥተው የራሳቸውን ገዳም አበጁ ርዝመቱ 5 አግድመቱ 2 ስፋቱ 3 ክንድ ነው በር የለውም ቀዳዳ እንጂ በዚህ ገዳም ውስጥ ሳይቀመጡ ሳይተኙ ያለመብልና መጠጥ ቆዳቸው ከአጥንታቸው እስኪጣበቅ 45 ዓመት በተጋድሎ ኖረዋል፤ ብዙ በሽተኞች ወደ እርሳቸው እየመጡ ይፈወሱ ነበር። አጼ ካሌብ በየመን ናግራን ክርስቲያኖችን ነጻ ለማውጣት ሲዘምቱ እኚህ አባት ጋር መጥተው ተባርከው ዘመቱ ድል አድርገው ሲመለሱም መንግስቴን አልፈልግም ብለው በእኚሁ አባት እጅ ነው የመነኮሱት። አቡነ ጰንጠሌዎን የእረፍት ቀናቸው ሲደርስ ጌታችን ተገልጦ በርካታ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል ጥቅምት 6 ቀንም አርፈዋል፤ ዛሬ ገዳማቸው የበረከት ቦታ ብቻ ሳይሆን የቱሪስትም መስህብ ነው። ከጻድቁ በረከት ያሳትፈን
LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment