Tuesday, November 5, 2013

ጥቅምት 23

ጥቅምት 23
በዚህች ቀን የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባ ዮሴፍ አረፈ፤ ይህ አባት ከደጋግ ክርሰቲያኖች ወገን ነው፤ ወላጆቹ በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት፤ ዲቁናን ቅስናን ተቀበላ በ 20 ዓመቱ መነኮሰ ገዳመ አስቄጥስ ገብቶ ለ 39 ዓመት በተጋድሎ ኖረ። ከዚህ በኃላ እንዲህ ሆነ 51ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ሲሞት አባቶች ማንን እንሹም ብለው አሰቡ፤ አባ ዮሴፍንም ለመሾም ከእግዚያብሔር ምልክትን አገኙ ወደ ገዳሙ ሄደው ተገናኙት፤ በመልካም መስተንግዶ በበዓቱ አስተናገዳቸው፤ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ አድርገን ልንሾምህ ነው ይሉታል፤ እኔ ኃጢያተኛ ነኝ አይሆንም ይላቸዋል፤ ስንክሳሩ እንደሚለው በግድ አስረው ወደ እስክንድርያ ወሰዱት 52ኛ ሊቀ ጳጳስም አድርገው ሾሙት ይላል፤ የሚገርም ነው የዚህ ዘመን ፍጹም ተቃራኒ ማለትም አይደል ባልንጀራን እስር ቤት ከቶ እኔ ልሾም እኔ ልሾም የምንል ትውልዶች የበቀልንበት ዘመን፤ አባ ዮሴፍ አስረው እንደሾሙት እርሱም በእግዚያብሔርና በሰው ፍቅር ታስሮ ለ 19 ዓመት መንጋውን ተግቶ ጠበቀ ድሆችን እረዳ፤ ሀይማኖቱን አጸና በ 78 ዓመቱ በዛሬዋ ቀን አረፈ። ከቅዱስ ጊዮርጊስና ከአባ ዮሴፍ በረከት ያሳትፈን።
LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment