Thursday, January 30, 2014

ጥር 22


ጥር 22 የቅዱስ ኡራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፤ ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን የመነኮሳት አባት ታላቁ ጻድቅ አባ እንጦንስ የእረፍት ቀኑ ነው፤ ይህ አባት ወላጆቹ በሀብት የከበሩ ነበሩ እነርሱ ሲሞቱ ንብረቱን በሙሉ ለድሆች መጽውቶ አናምስት አናምርት አካይስት አቃርብት ካሉበት፤ ነቀዐ ማይ ልምላሜ እጽ ከሌለበት ፤ ዘር ተክል ከማይገኝበት ከጽኑ በርሃ ገባ በዚያም በተጋድሎ መኖር ጀመረ ሰይጣናት በዘንዶ በጊንጥ እጅግ በሚያስፈሩ አውሬዎች እየተመሰሉ ያስፈራሩት ጀመር “አባቱ አዳም ከገባበት እገባለሁ ብሎ ነው እኮ ከዚህ የመጣው” እያሉ ይስቁበት ይሳለቁበት ነበር እየደበደቡ ስቃይ አጸኑበት እርሱ ግን በትህትና እናንተ ብዙ እኔ አንድ እናንተ ኃያላን እኔ ደካማ እናንተ ረቂቃን እኔ ግዙፍ በአምላኬ ኃይል ካልሆነ እንዴት እችላቹዋለሁ እያለ በትህትና ተዋጋቸው ነገር ግን መከራውን መቋቋም ሲያቅተው በቃ ወደ ከተማ ልመለስ ብሎ አንድ እግሩን ከውስጥ አንድ እግሩን ከውጭ አድርጎ ሲያወጣ ሲያወርድ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል የሰሌን ቆብ አድርጎ የሰሌን ልብስ ለብሶ የሰሌን መቋሚያ ይዞ ከበሩ ፊት ለፊት ጸሎት ሲያደርግ አየ የዚህን መልአክ ፍጻሜውን ሳላይማ አልሄድም ብሎ ቆመ መልአኩ መጀመሪያ ለሥላሴ አንድ ስግደት ሰገደ ከዚያም ጸሎት አደረሰ ወንጌል አነበበ በመጨረሻም አንድ አቡነ ዘበሰማያት ብሎ ሦስት ጊዜ ሰገደ እንደዚህ እያደረገ 12 አቡነዘበሰማያትን አድርሶ 36 ጊዜ ሰገደ በእያንዳንዱ ሶስት ሶስት ጊዜ፤ ከዚያም ቁጭ ብሎ የያዘውን ሰሌን መታታት (መስፋት) ጀመረ፤በ 3፤ በ 6፤ በ 9 እና በ 11 ሰዓትም እንደዚሁ እያደረገ አሳየውና እንጦንስ ከሚመጣብህ ከሰይጣን ጾር ለመዳን እኔ እንዳደረግሁት ዘወትር አድርግ ብሎ ስርዓተ ምንኩስናን አስተምሮት ከእርሱ ተሰውሯል፤አባ እንጦንስም መልአኩ እንዳሳየው ጸሎት እያደረገ ሰሌን እየሰፋ በተጋድሎ ኖሯል፤ ከእለታት በአንዱ ቀን ከአባ ጳውሊ ጋር ተገናኝተው መጨዋወት ጀመሩ ይህን ቆብ ማን ሰጠህ ይልዋል ከእግዚያብሔር ነው የተቀበልኩት አለው፤ አባ ጳውሊ አደነቀ “ይልቅስ እስኪ ከኔ በኃላ እንደዚህ ዓይነት ቆብ የሚያደርግ መኖር አለመኖሩን ወደ እግዚያብሔር ጸልይሊኝ ይለዋል፤ አባ ጳውሊ ሲጸልይ ነጫጭ ርግቦችን ያያል ደስ አለው ከአንተ በኃላ ያንተን ፈለግ የሚከተሉ ልጆችህ ይነሳሉ ይለዋል እስኪ እባክህን ደግመህ ጸልይሊኝ ሁሉም የኔ ልጆች ናቸውን ይለዋል ሲጸልይ አንዳንድ ጥቁር ነገር የተቀላቀለባቸውን ያያል ገረመው ሁሉም ጻድቃን አይደሉም ጽድቅና ኃጢያትን የሚቀላቅሉም አሉበት ይለዋል፤ ለሶስተኛ ጊዜ ቢጸልይ ጥቋቁር ቁራዎችን ይመለከታል ድምጹን አሰምቶ ያለቅሳል ምነው ይለዋል በኃለኛው ዘመን የሚነሱት መነኮሳት ሹመት ሽልማት ፈላጊ፤ ገንዘብን የሚወዱ፤ ፍቅር የሌላቸው ትዕቢተኞች ናቸው በፈረስ በበቅሎ ነው የሚሄዱት፤ከመኳንንት ጋር ቁጭ ብለው ኃጢያትን የሚዶልቱ ናቸው አለው እስኪ እባክህን በንስሃ ይጠራቸው እንደሆነ ጠይቅሊኝ ይለዋል ይዚህ መልስ አልመጣለትም ይላል መጽሐፈ መነኮሳት 2ኛው ወይንም ፊሊክስዩስ፤በነገራችን ላይ በፈረስና በብቅሎ ነው የሚሄዱት ያለው ያኔ በ 3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ስለሆነ ነው ለዚህ ዘመን ስንመነዝረው ሐመርና ኮብራ መሆኑም አይደል። አባ እንጦንስ የእረፍት ቀኑ ሲደርስ ጌታችን ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ገብቶለታል ጥር በባተ በ 22ኛው ቀን አርፏል። ከመልአኩ ቅዱስ ኡራኤል ከአባ እንጦንስ በረከታቸውን ያሳትፈን።

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment