Monday, February 3, 2014

ጥር 25

ጥር 25 በዚህች ቀን በገድል የተጸመደ የከበረ ጴጥሮስ አረፈ። ይህ አባት አስቀድሞ ቀራጭ ነበር ርህራሄ የሌለው ጨቃኝ ልቡ የደነደነ ኃጢያተኛ፤ ይህን ጭካኔውን አይተው "እኩይ ዘአልቦ ምህረት" የሚል ቅጽል ስም አውጥተውለት ነበር። ከዕለታት በአንዱ ቀን ግን እንዲህ ሆነ አንድ ደሃ ምስኪን ቤቱ በራፍ ቆሞ በእንተ ስማ ለማርያም ብሎ ምጽዋት ይለምነዋል ደሃው ከፊቱ ቶሎ እንዲሄድለት እንጀራ ጠቅልሎ ይወረውርለታል፤ ምስኪኑም ተቀብሎ ወደ ማደሪያው ሄደ። በዚያች ሌሊት ተኝቶ ሳለ በህልሙ ነፍሱ ወደ ሰማይ ሄዳ ለፍርድ ቆማ ያያል በግራ በኩል ስይጣናት በቀኝ በኩል ነጫጭ የለበሱ መልአክት ቆመዋል በመካከል ሚዛን አ...ለ ሚዛኑ በግራ በኩል አዘንብሏል በቀኝ በኩል በዶ ነው፤ " ምን ይሻላል ሚዛኑ እኮ ባዶ ነው" አሉ መልአክት ከመካከላቸው አንዱ መልአክ ተነስቶ ይህቺ አንድ እንጀራ አለች እርሷን ላስቀምጣት አላቸው፤ በዚህ ሁሉ ኃጢያቶች ይህቺ ብቻ እንጀራ ምን ትሰራለች አሉት፤ ማቴ 25 ፤ 35 በዚህን ጊዜ ደንግጦ ከእንቅልፉ ነቃ አልዋለም አላደረም ሀብቱን ንብረቱ፤ ቤቱን ጥሪቱን ሁሉ ሸጦ ለድሆች ሰጠ በዚህም አላበቃም ራሱን በባርነት ሸጦ ገንዘቡን ለድሆች መጸወተ፤ በዙዎች ሲያመሰግኑት ሲያደንቁት ውዳሴ ከንቱ ፈርቶ በገዳመ አስቄጥስ ከአባ መቃርስ ገዳም ገብቶ መነኮሰ በዚያም ለብዙ ዓመት በተጋድሎ ኖሮ በዛሬዋ ዕለት በክብር አረፈ። ኃጢያተኛ ተመልሶ በህይወት እንዲኖር እንጂ ሞቱን የማይሻ እግዚያብሔር ይመስገን፤ እኛንም ከአባ ጴጥሮስ በረከት ያሳትፈን።

LIKE OUR PAGE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment