Thursday, March 27, 2014

መጋቢት 13

በዚህች ቀን ፵ ሐራ ሰማይ በሰማዕትነት አረፉ። 
ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ነው በወቅቱ በሮም ነግሶ የነበረው ደግሞ አረመኔው ንጉስ ሉክ
ያኖስ ነው፤ መኮንኑ ግሪኮልዮስ ይባላል። ክርስቶስን ክዶ ለጣኦት እንዲሰግድ ህዝቡ ላይ የመከራ ቀንበር ጫኑበት፤ ብዙዎች ሞቱ ብዙዎችም ካዱ። የንጉሱ ወታደሮች የነበሩት በጀግንነታቸው የሚታወቁት አገራቸውን በውትድርና ያገለገሉት ፵ ሐራ ሰማይ ግን እኛ የሰማያዊው ንጉስ የእየሱስ ክርስቶስ ወታደሮች ነን ለጣኦት አንሰግድም አሉ። ለዚህም ነው ፵ ሐራ ሰማይ የተባሉት “የሰማያዊ ንጉስ ወታደር ተከታይ” ማለት ነው፤ ብዛታቸው 40 ነው። ከዚህ በኃላ ልዩ ልዩ ጸዋትኦ መከራ... አጸኑባቸው ይህን ሁሉ ታገሱ፤የመጨረሻ መከራቸው ግን ለየት ያለ ነበር፤ ሰውነትን የሚቆራርጥ እጅግ ቀዝቃዛ ወደሆነ የበረዶ ባህር ውስጥ መጣል መወርወር፤ ተጣሉ ተወረወሩም ስቃዩ ቅዝቃዜው እጅግ ጸናባቸው፤ ቀናት፤ ሳምንታት፤ ወራት ተቆጠሩ ወታደሮች ዙሪያውን ከበው እየተመለከቷቸው ነው፤ የሚገርመው የመጨረሻው ቀን ላይ አንዱ ስቃዩ ሲጸናበት ከባህሩ ወጣ 39 ቀሩ ነገር ግን 40 የብርሃን አክሊላት ወርዶ በራሳቸው ላይ አረፈ አንዷ ብቻ አየር ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ይህንን የተመለከተ ወታደር ሮጦ ወደ ባህሩ ገባ ከሰማዕታቱ ጋርም ተቀላቀለ፤በበነጋው ሁሉንም በሰይፍ ገደሏቸው ይህም መጋቢት 13 ቀን ነው። ከሰማዕታቱ በረከት ያሳትፈን። 
ስንክሳር፤ ገድለ ሰማዕታት

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment