Thursday, March 27, 2014

መጋቢት 17

በዚህች ቀን የአገረ ሮሜው ቅዱስ አባ ቴዎቅሪጦስ በሰማዕትነት አረፈ። ገና የ15 ዓመት ብላቴና ሳለ ዓላውያን ለጣኦት እንዲሰዋ ግድ አሉት፤ ከጌታዬ ከእየሱስ ክርስቶስ በቀር አምላክ የለም አላቸው፤ እየደበደቡ ንጉሱ ጋር አቀረቡት፤ ንጉሱም ለጣኦት ስገድ አለው፤ ንጉሱንም ጣኦታቱንም ዘለፋቸው፤ ንጉሱ ተቆጣ አፍንጫውን ቆረጠው፤ ወደ ገደል ወረወረው፤ ስጋው እስኪበጣጠስ አጥንቶቹ እስኪሰባበሩ አስደበደበው፤ እንዲያውም የሰደባቸው የዘለፋቸው አማልክቶቻችንን ተበቅለው ያጥፉት ብሎ ጣኦት ቤት አስገብተው ዘጉበት፤ ይህ ቅዱስ ግን ጣኦቶቹ ላይ ያለውን ወርቅ እያወለቀ በስውር ወጥቶ ለጦም አዳሪዎችና ለምስኪኖች... አከፋፍሎ ይመለሳል፤ በሩ እንደቀድሞ ይዘጋል ሐዋ 16፤26 ጳወሎስና ሲላስ የወህኒ ቤቱ በር በመዝሙር እንደከፈቱት ልብ ይሏል። ከአንድ ሳምንት በኃላ ሊያየው ቢመጣ ጣኦታቱ ተሰባብረው ወድቀው ቅዱሱ ሲዘብትባቸው አገኘው 1ኛ ሳሙ 5፤4 በዚህም ተቆጣ የሆድ እቃው እስኪታይ አስደበደበው፤ ወደ መጫወቻ ቦታ አስገቡት አንበሶች ለቀቁበት፤ አንበሶቹ ግን ቁስሉን ላሱለት ዳን 6፤22። ዳግመኛ ልዩ ልዩ መከራ አደረሰበት በመጨረሻም በዛሬዋ ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት እርሱም የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከሰማዕቱ በረከት ያሳትፈን።

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment