Thursday, March 27, 2014

መጋቢት 19

በዚህች ቀን የብርሃናተ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር የሆነው ሐዋርያው አርስጣባሉ በሰማዕትነት አረፈ። ይህ ሐዋርያ ቁጥሩ ከ 72ቱ አርድእት ነው፤ በአምሳኛው ቀን ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ አብሮ ነበር፤ በኃላም ቅዱስ ጳውሎስን ተከትሎ አገር ለአገር እየዞረ ወንጌልን አስተማረ፤ ቅድስናውን በተመለከቱ ጊዜ አባቶቻችን ሐዋርያት አብራጣብያስ በሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ አድርገው ሾሙት እርሱም ወረደ ተወለደ ሞተ ተቀበረ ተነሳ ዳግም ለምጽአት ይመጣል፤ በእርሱ ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ይፈረድበታል እያለ ክርስቶስን ሰበከላቸው ብዙዎች አመኑ ተጠመቁም ቤተክርስቲያን አንጾላቸው ዲያቆን ካህን ሾሞላቸው ሲያበቃ ወንጌልን ለማስፋት ወደ ሌላ አገር ሄደ፤ በዚያም ሲሰብክ ሲያስተምር ዓላውያን ጣኦት አምላኪዎች ያዙት በብዙም አሰቃዩት በዛሬዋ ቀንም ገደሉት፤ እርሱም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፤ ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች መልእክትን ሲጽፍ የዚህን አባት ስም አንስቶ ሰላምታ አቅርቦለታል ሮሜ 16፤10። ከቅዱስ ገብርኤልና ከሐዋርያው አርሰጣባሉ በረከት ያሳትፈን። 

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment