Monday, June 9, 2014

ግንቦት 28

ግንቦት 28 በዚህች ቀን ዓለምን ንቃ የተወች ገዳማዊቷ ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ አረፈች። በበርሃ የሚኖረው አባ ዳንኤል ስለዚህች ሴት እንዲህ አለ፤ ከዕለታት በአንዱ ቀን በጨረቃ ብርሃን በርሃውን አቋርጬ ስጓዝ ተራራ ላይ የተቀመጠ ሰው አየው ግርማው ያስፈራል መላ ሰውነቱን ጸጉር ሸፍኖታል ሰው ይሁን መንፈስ ልረዳ ቀረብኩት እርሱ ግን እንደተመለከተኝ ሮጦ የተሰነ...ጠቀ አለት ውስጥ ገብቶ ተደበቀ፤ ሰው እንደሆነ አወቅኩኝ፤ አባቴ በረከትህን እሻለሁና ወደ ዋሻው አስገባኝ ብዬ ለመንኩት፤ እርሱ ግን ወደኔ መግባት አይቻልህም አለኝ፤ የሴት ድምጽ ነው፤ ለምን አለኳት፤ እርቃኔን ነኝ አለችኝ፤ የለበስኩትን አጽፍ አኖርኩላት እርሱን ለብሳ ወጣች፤ ታሪኳን ሁሉ ነገረችኝ፤ በዘንቢል ሽንብራ በኮዳ ውኃ ይዛ ከወላጆቿ ቤት እንደወጣች ለ 38 ዓመት በኤርትራ በርሃ ሰው ሳታይ ብቻዋን በተጋድሎ እንደኖረች ነገረችኝ እኔም ጻፍኩት ይለናል፤ ይህች ቅድስት እናት ኢትዮጰያዊት እንደሆነች የትውልድ ቦታዋም ሸዋ ውስጥ ተጉለት እንደሆነ በአገራችን አንድ ገዳም እንዳላት ሊቀ ብርሃናት መርቆርዮስ አረጋ "የኢትዮጰያ ተወላጆች ቅዱሳን" በሚል መጽሐፋቸው ጠቅሰውታል፤ ስንክሳሩም ሰርቶላታል፤ ግንቦት 28 በዛሬዋ ቀን እረፍቷ ነው። በረከቷን ያድለን።

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment