Monday, July 14, 2014

ሐምሌ 8 እንኳን አደረሳችሁ

በዚህች ቀን ከሮም ነገስታት ወገን የሆነው አባ ኪሮስ አረፈ፡፡ አባታቸው በሞተ ጊዜ ታላቅ ወንድማቸው ቴዎዶሲዎስ በሮም ነገሰ፡፡ አባታችን አቡነ ኪሮስ ግን ሀብት ንብረታቸውን ትተው ወደ ገዳም ሄዱ ከአባ በቡኑዳ እጅም ምንኩስናን ተቀበሉ በታላቅ ተገድሎ ኖረው በዛሬዋ ዕለት በክብር አረፉ፡፡ አባታችን አቡነ ኪሮስ በመዲናችን አዲስ አበባ በኮተቤ መስመር በስማቸው ታላቅ ቤተክርስቲያን አላቸው ሐምሌ 8 ታቦታቸው ወጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፡፡ ልጅ የሌላቸው እናትና እህቶቻችን ገድላቸውን አዝለው ልጅ እንዲሰጧቸው ስለት ይሳላሉ በዓመቱም ልጅ አዝለው መጥተው ስለታቸውን ይከፍላሉ፡፡ ይህንንም በአይናችን አይተን በጆሯችን ሰምተን ይኸው እንመሰክራለን ፡፡ በረከታቸው ይደርብን

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment