Thursday, April 7, 2016

መጋቢት 29

መጋቢት 29 

ቀን በዕለተ ዕሁድ እግዚያብሔር ዓለምን መፍጠር ጀመረ። እነሆ ዓለም ከተፈጠረ ዘመን ከተቆጠረ 7508 ዓመት ሆነው፤ ዘፍ 1፤1። ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን ዓለምን ለማዳን የድህነት ስራውን መስራት የጀመረበት ቀን ነው፤ ይህም ጽንሰቱ ነው። መጋቢት 29 በዕለተ ዕሁድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ሲሆን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ጎንበስ ቀና እያለ ተፈስሒ ኦ ምል...ዕተ ጸጋ ተፈስሂ ኦ ምልዕተ ክብር...ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ እያለ ሲያመሰግናት ሲያረጋጋት ቆይቶ ልክ "እነሆ ትፀንሻለሽ" ሲላት አካላዊ ቃል በማህጸኗ አደረ፤ ሉቃ 1፤28። ከላይ ሳይጎድል ከታችም ሳይጨመር እሳተ መለኮት በማሕጸኗ አደረ በማይመረመር ግብር ፍጹም ስጋንም ተዋሃደ። ይህ ቀን እጅግ ታላቅ ዕለት ነው፤ ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው አራት ኪሎ በዓለወልድ ቤተክርስቲያን ታቦተ ህጉ ወጥቶ ይነግሳል። ዳግመኛ በዛሬዋ ዕለት ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት ቀን ነው፤መጋቢት 29 በዕለተ ዕሁድ ከሌሊቱ 6 ሰዓት። ይህንንም ቀን ጥንተ ትንሳኤው ብላ ቤተክርስቲያን አስባው ትውላለች። ሰውን ለወደደ ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን። ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።

No comments:

Post a Comment